Widgetized Section

Go to Admin » Appearance » Widgets » and move Gabfire Widget: Social into that MastheadOverlay zone

አዲስ አበባ የአፍሪካ ፋይናንስ ማዕከል መሆኗ ተገለጸ

ህዳር 12፣ 2009

ኢትዮጵያ፣ ሩዋንዳ እና ናይጀሪያ የአፍሪካ የፋይናንስ ማዕከላት እየሆኑ መምጣታቸውን የአፍሪካ ቢዝነስ ትራቭል አሶሴሽን አስታወቀ፡፡
adis-is-part-of-african-finance
አዲስ አበባ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ዕድገት ተመራጭ መዳረሻ መሆኗን የአፍሪካ ቢዝነስ ትራቭል አሶሴሽን መስራች ሞኒክ ስዋርት ገልጻለች፡፡

በተጨማሪም የናይጀሪዋ ሌጎስ እና የሩዋንዳዋ ኪጋሊ የአፍሪካ ፋይናንስ ማረፊያ የሆኑ ከተሞች መሆናቸውን ዘገባው ያስረዳል፡፡

የኢትዮጵያ እና የሩዋንዳ ቱሪዝም ዕድገት ለማዕከልነታቸው ከፍተኛ ሚና መጫወቱን በዘገባው ተገልጿል፡፡

ኬንያ፣ ሴኔጋል እና ቡርኪናፋሶም በፋይናንስ ማዕከልነት ከተቀመጡ ሀገራት ቀጣዮቹን ደረጃ ይዘዋል፡፡

ደቡብ አፍሪካ በአህጉሩ የግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ሀገራት ተርታ ብትመደብም የአህጉሩ የፋይናንስ ማዕከል ያለመሆኗ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡

የአፍሪካ ትራቭል አሶሴሽን የአፍሪካን የፋይናንስ ገጽታ ላይ አትኩሮ ጥናት የሚያወጣ ተቋም ነው፡፡