Widgetized Section

Go to Admin » Appearance » Widgets » and move Gabfire Widget: Social into that MastheadOverlay zone

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ


አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከ20 ዓመታት በኋላ በኤርትራ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

አምባሳደር ሬድዋን ቀደም ሲል በአየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኤርትራ ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር አበክሮ የሚሠራ መሆኑን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።