Widgetized Section

Go to Admin » Appearance » Widgets » and move Gabfire Widget: Social into that MastheadOverlay zone

ብሄራዊና የክልል ደህንነት የፀጥታ ምክር ቤቶች የጋራ እቅድ ወጣ


አዲስ አበባ ፣ ህዳር 1 ፣ 2010 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገሪቱን የሰላም እና ፀጥታ ነባራዊ ሁኔታዎች ያገናዘበ የብሄራዊ እና የክልል ደህንነት ፀጥታ ምክር ቤቶች የጋራ እቅድ ወጣ።

ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሃይሎች እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት አዛዦች ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተወያይተዋል።

ለቀጣይ አንድ አመት ሀገሪቷ የምትመራበት ወጥ የሰላም እና ፀጥታ እቅድ የወጣ ሲሆን በእቅዱ ላይም ውይይት ተደርጎ ስምምነት ላይ መደረሱን፥ የመከላከያ ሚኒስትሩና የብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሀላፊ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

ከዚህ ባለፈም ባለፈው አመትና በአሁኑ አመት በሃገሪቱ ያለው የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ ላይ ግምገማ መደረጉን ያነሱት አቶ ሲራጅ፥ የአስቸኳይ የጊዜ አዋጁ ከተነሳ በኋላ ከአንዳንድ አካባቢዎች በስተቀር የሀገሪቱ ሰላም እና ፀጥታ ጥሩ የሚባል መሆኑን ገልጸዋል።

የሀገሪቱን አሁናዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ታሳቢ ተደርጎ እቅዱ መውጣቱን የተናገሩት አቶ ሲራጅ፥ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ድረስ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

አሁን ላይ ሀገሪቱ የምታካሂዳቸው የልማት ስራዎች እንዳይደናቀፉ የፀጥታ ሀይሉ ከመቸውም በላይ እየሰራ እንደሚገኝም ነው የገለጹት።

አያይዘውም በኦሮሚያ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ድንበር አካባቢ በተስተዋለው ግጭት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ የፀጥታ ሀይሉ እቅደ አውጥቶ እየሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

በተጨማሪም በግጭቱ እና ሁከት የተሳተፉ የመንግስት አካላት እና ግለሰቦችን የማጣራት ስራ እየተከናወነ ሲሆን፥ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ለህግ ቀርበው ወሳኔ ያገኛሉም ነው ያሉት።

የእቅዱ ተግባራዊነት በየጊዜው ግምገማ ተደርጎበት የሃገሪቱ ሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ለህዝቡ ይፋ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።